የሰንበት ት/ቤት Søndagsskole

የደብሩ ፈለገ ሕይወት የሰንበት ትምህርት ቤት ዓመታዊ በዓሉን አከበረ

እሑድ ግንቦት 27 ቀን ከሰንበት የቅዳሴ ሥነ ሥርዓት በኋላ የደብሩ ፈለገ ሕይወት የሰንበት ትምህርት ቤት ዓመታዊ ክብረ በዓሉን አክብሮ ውሏል፡፡ በዕለቱም ከተዘጋጁት መርሃ ግብሮች ውስጥ የሰንበት ት/ቤቱ ዓላማ፣ ደንብና መመሪያ የቀረበ ሲሆን በተጨማሪም የዓውደ ርዕይ፣ የሥነ ጽሑፍ፣ የትምህርታዊ ጭውውት፣ የጥያቈና መልስ እንዲሁም በሥዕል የተደገፈ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክንን ቅዱሳን መካናትቅዱሳን ንዋያትቅዱሳን መጻህፍትናቅዱሳን ሥዕላትን የሚያሳዩ ማብራሪያዎች ቀርበዋል፡፡
በዕለቱም ሰንበት ት/ቤቱን ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት የሚያገለግሉ የአመራር አካላት ዕጩዎችን አቅርቦ አስጸድቋል፡፡

 

የሰንበት ት/ቤት መዋቅር

img_7394