Bli medlem / የቤተ ክርስቲያናችን አባል ይሁኑ
Alle uansett nasjonalitet og hudfarge som er troende i den kristne ortodokse tewahedo tro kan bli medlem etter å ha lest, oppfattet Menighetens stiftelsesdokument og Grunnordring og levert påmeldingsskjema i utfylt stand.
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የኦስሎ ማሕደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ አባል ለመሆን ይመዝገቡ ዘንድ በታላቅ መንፈሳዊ አክብሮት ጥሪውን ያቀርባል።
በአባልነት የሚገኝ ጥቅም
ማንኛውም ሰው በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ከተጠመቀ በኃላ ክርስቲያን ይሆናል ክርስቲያን የሚሆነው በክርስቶስ በማመን ሲጠመቅ ነው። ከጥምቀትም በኃላ የሚከተሉትን ያገኛል
- እግዚአብሔር በሚሰጠው የልጅነት ጸጋ የመንግሥቱ ወራሽ ይሆናል፤
- የበደልን እና የኃጢያትን ሥርየት ይቀበላል፤
- በቤቱ ልጅና ወራሽ በመሆን ከእርሱ በሆነ ጸጋ የመንፈሳዊ በረከት ሁሉ ተካፋይ ይሆናል፡
በመሆኑም ጥንታዊና ታሪካዊ በሆነች በአንዲት የተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የእምነት ጥላ ሥር በመሆን በአጥቢያችን ከምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ጋር ህብረት ሲኖረው የሚያገኘው የማይቋርጥ ጸጋ ነው። ስለዚህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኖርዌይ ኦስሎ የማሕደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ ከላይ ከተገለጸው መንፈሳዊ በረከት በተጨማሪ የሚከተለውን መንፈሳዊ አገልግሎት ትሰጣለች፦
- ጥምቀት፤ ተክሊል እና ጸሎተ ፍታት
- የካህናት ምክር
- ለህጻናትና ለወጣቶች ታሪክን፣ ባህልን፣ ቋንቋንና ክርስቲያናዊ ግብረገብነትን ማስተማር
- የአባልነት ማስረጃ ለሚያስፈልጋቸውና በቤተ ክርስቲያኑ አስተዳደር ውስጥ መሳተፍ፤ መመረጥና መመረጥ፤
በዚህ መሠረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማሕደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም አባል ለመሆን ይመዝገቡ ዘንድ በታላቅ መንፈሳዊ አክብሮት እንጠይቃለን። ለአሰራር ቅልጥፍና በዚሁ ድኅረ ገጽ የሚገኘውን የአባልነት ፎርም በመሙላት ቅጹን ሞልተው በሜይል አድራሻቸን አባሪ በማድረግ ቢልኩልን በቀላሉ መመዝገብ እንችላለን፡፡ በማንኛው የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ አገልግሎት ጥያቄ ካልዎት መልስ እንሰጣለን።
የአባልነት መመዝገቢያ ቅጽ
ማሳስቢያ፡ የፔርሶን ነምበር ባሁን ሰዓት መሙላት አያስፈልግም፡፡ ከመረጃ አጠባበቅ ሥነ ሥርዓት አንጻር ፎርሙን ሞልተው ከላኩ በሁዋላ በሰጡት የሞባይል አድራሻ የቤ/ክርስቲያኑ ሃላፊ (forstander) ደውለው ይቀበልዎታል፡፡ የአባልነት ፎርምና ማህደር የሚቀመጠው በቤተ ክርስቲያኑ ሃላፊ (forstander) እጅ ብቻ ነው፡፡
Velsignelser ved Medlemskap
En person som tror på Kristus og blir døpt i Faderen, Sønnen og Den Hellige Ånds navn blir kristen.
I kraft av dåpen er en kristen utstyrt med å arve Guds rike gitt til hans barn, motta nåde fra svakheter og synder, og som hans barn og arvinger til hans rike, delta i den hellige begavelse gitt i sin visdom.
Når vi samles under paraplyen av den entydige, eldste og historisk ortodokse Tewahedo kirke, skal vi dra nytte av de ubegrensede velsignelser begavet til oss.
I tillegg til de ovennevnte åndelige velsignelser, gir den Etiopisk ortodokse kirke Mahidere Sibiha Kidist Lideta Le-Mariam kirke i Oslo følgende åndelige tjenester til sine medlemmer:
1. Dåp, bryllup og minnegudstjeneste.
2. Counseling av presteskapet.
3. Lære og oppdra barn i den kristne etikk m.m.
Vi ber deg dermed om å melde deg på ved å fylle ut påmeldingsskjemaet via lenken under. Ta kontakt via ”kontakt oss” dersom det er noe du lurer på.
NB! la personnummer feltet stå blank. Dette ordner man sammen med forstander av kirken i etterkant av påmeldingsprosessen.